EN አማ
Back to News
2026 Finote Damot Polytechnic College

2026 Finote Damot Polytechnic College

Sintayehu  |  June 22, 2026 at 6:45 PM  |  29 days ago  |  49 views


የፍኖተ ዳሞት ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ከደ/ማርቆስ ብቃት ማረጋገጫ ማዕከል አስተባባሪዎች እና ከመዛኞች ጋራ ተመዛኝ ተማሪዎችን በመያዝ ለችግኝ መትከያ የሚሆን የጉርጓድ ቁፋሮ ስራ ተከናውኗል።

ሰኔ15/2018ዓ.ም

👉ኮሌጁ በያዝነው የክረምት ወራት ከአራት ሺ/4000/በላይ ችግኞችን ለመትከል በእቅድ የያዘ ሲሆን በዛሬው ዕለት ከ120በላይ ተሳታፊዎች በተገኙበት ሁለት መቶ/200/ የችግኝ መትከያ ጉርጓድ መቆፈር ተችሏል። 
👉ይህ ተግባር ተጠናክሮ እንደሚቀጥልና በተዘጋጀው ስፍራ ችግኞችን በመትከል የተያዘውን ዕቅድ ማሳካት እንደሚገባ በኮሌጁ ም/ዲን "በአቶ ቸኮል አየለ" መልዕክት ተላልፏል።
👉ተመዛኝ ተማሪዎች እና ተመራቂዎች በዚህ ታላቅ ተግባር ላይ በመሳተፍ አሻራቸውን ማስቀመጣቸው ጥሩ አጋጣሚ እንደሆነ እና ታላቅ ደስታ እንደፈጠረላቸውም ገልፀዋል።

15/10/2018ዓ.ም
ፍ/ዳ/ፖ/ቴ/ኮሌጅ

Previous | Next